Home | About us| Music | Comedy | Docs | Film | Orthodox Mezmur | Protestant Mezmur | News | Amharic | Business | Feeds | Links
If you cant see this page, download one of the following two fonts.
1. Click here for windows systems.
2.Click here for non-windows systems.

የናይልን ልጅ ልማትና ፍቅር ጠማው

“የዓባይን ልጅ ውኃ ጠማው” ያላልነው ጥቁሩንም ነጩንም ዓባይ በአንድነት ለማጠቃለል ስለፈለግን ነው፡፡ ናይል ሁሉንም ስለሚያጠቃልል ነው፡፡

Posted on 22 February 2012 | 12:02 am

የኢጋድ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ምን እየፈየደ ነው?

በአፍሪካ የሚከሰቱ ግጭቶች በርካታ መንስዔዎች የሚኖሩዋቸው ቢሆንም፣ በአብዛኛው በድንበር ውዝግብ የሚከሰቱ ናቸው፡፡ በሁለት አገሮች ድንበር አካባቢ የሚከሰቱ ግጭቶች መነሻቸው፣ ሁለትና ከዚያ በላይ ማኅበረሰቦች ለሁለት ተከፍለው መኖራቸው መሆኑን የግጭት ተመራማሪዎች ያመለክታሉ፡፡

Posted on 22 February 2012 | 12:01 am

አንዱአለም አራጌ በፍርደኛ ድብደባ ተፈጸመባቸው

“የአቶ አንዱአለም ደኅንነት አደጋ ላይ ነው”  አንድነት ፓርቲ

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የሚገኙት አቶ አንዱአለም አራጌ የካቲት 7 ቀን 2004 ዓ.ም. ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ገደማ ለሕይወታቸው የሚያሰጋ ከባድ ድብደባ የተፈጸመባቸው መሆኑን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ አስታወቀ፡፡

Posted on 21 February 2012 | 11:59 pm

አምስት የመንግሥት ተቋማት የሕዝብን አመኔታ አጥተዋል ተባለ

የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ትናንት ይፋ ባደረገው ጥናት ፍርድ ቤቶች፣ ፖሊስ፣ የኢትዮጵያ ጉምሩክና ገቢዎች ባለሥልጣን፣ የወረዳ መስተዳድር አካላትና ማዘጋጃ ቤቶች የኅብረተሰቡን አመኔታ አጥተዋል አለ፡፡

Posted on 21 February 2012 | 11:57 pm

ማሞ ውድነህ ታመዋል

ታዋቂውና አንጋፋው ደራሲ አቶ ማሞ ውድነህ ጤንነታቸው ታውኮ አልጋ ከያዙ አንድ ወር ሆኗቸዋል፡፡ በቅድሚያ ዳግማዊ ምኒልክ ቀጥሎም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታሎች ሕክምና ቢከታተሉም ለተጨማሪ ሕክምና ወደ ኢንተርናሽል የልብና ልብ ነክ ደዌዎች ሆስፒታል ከገቡ ሦስት ቀኖች አስቆጥረዋል፡፡

Posted on 21 February 2012 | 11:55 pm

ቢፒአር በመንግሥታዊ ተቋማት ዓላማውን መሳቱ ተገለጸ

‹‹ተቋም ሲወድቅ የመጀመርያው ተጠያቂ የበላይ ኃላፊው መሆን አለበት›› አቶ ጁነዲን ሳዶ

መሠረታዊ የሥራ ሒደት ለውጥ (ቢፒአር) በአብዛኛው ለግሉ ሴክተር የተዘጋጀ በመሆኑ፣ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች እንዴት እንደሚጠቀሙበት በቂ ትኩረትና ዝግጅት ሳያደርጉበት ወደ እንቅስቃሴ በመግባታቸው፣ እንቅስቃሴውን በጥርጣሬ ውስጥ እንዲወድቅ ከማድረጉም በላይ፣ በተግባርም በበርካታ ጉዳዮች ላይ መፍትሔ ሊሰጥ አለመቻሉን ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ከትናንት በስቲያ አስታወቀ፡፡

Posted on 21 February 2012 | 11:54 pm

በአራት ኪሎ መልሶ ማልማት የግል ይዞታ ውዝግብ እያስነሳ ነው

በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 በተለምዶ እሪ በከንቱ በሚባለው ወይም ባሻ ወልዴ ችሎት ሁለት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች፣ ‹‹የግል ይዞታችን ሳይለካና ካሣ ሳይከፈለን ቤታችንን በላያችን ላይ ወረዳው እያፈረሰብን ነው፤›› አሉ፡፡

Posted on 21 February 2012 | 11:53 pm

የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ለደመወዝ ጭማሪ ጥያቄ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ ጠራ

በጥቅምት ወር 2004 ዓ.ም. በድሬዳዋ በተካሄደው የኢትዮጵያ መምህራን ጠቅላላ ጉባዔ እስከ ጥር 30 ቀን 2004 ዓ.ም. ድረስ የደመወዝ ጭማሪ እንዲደረግለት ጥያቄ ያቀረበው የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር፣ ጥያቄው ምላሽ ባለማግኘቱ ምክንያት በጉዳዩ ላይ ለመምከር ነገ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ ጠራ፡፡

Posted on 21 February 2012 | 11:52 pm

የአዲስ አበባ አስተዳደር ትልቁ ችግር ያልተገባ ጥቅም መስጠትና ማግኘት መሆኑ ተወሳ

“ኪራይ ሰብሳቢነት አገልግሎታችንን እየጎዳ በመሆኑ ለሕዝብ ሮሮ አጋልጦናል” ከንቲባ ኩማ ደመቅሳ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በልማትና በመልካም አስተዳደር ግንባታ ሥራዎች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደሩበት የሚገኙት፣ ያልተገባ ጥቅም የመስጠትና የማግኘት አመለካከትና ተግባር አለመወገድ መሆናቸውን አስታወቀ፡፡

Posted on 21 February 2012 | 11:51 pm

ለስኳር ልማት የሚያስፈልግ 100 ሺሕ ሔክታር ከሰው ንክኪ ነፃ ሊሆን ነው

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የስኳር ልማት ኮርፖሬሽንና የፓኪስታኑ ኩባንያ አል ሐበሻ ስኳር ሊያለሙ ያቀዱትን መቶ ሺሕ ሔክታር መሬት ከሰው ንክኪ ነፃ በማድረግ ሥራ ተጠምዷል፡፡

Posted on 21 February 2012 | 11:50 pm